የነጻነት ትግል መሰዋእትነት ብእርም ብቻ አይደለም ተግባርም እንጂ!
የጽሁፌ መነሻ Ato ያሬድ ሃይለ ማርያም ወረድ ብሎ ደግሞ የማይቀረው ማእረግ ያለበት ለ ሰባት አመት በኢትዮጵያ የሰበአዊ መብት ምክርቤት የሰራ በወያኔ ግፍ ከሚወዳት ሀገሩ በ97 አም ጭፍጨፋ የተሰደደ ከፈለጋችሁ ደግሞ በአውሮፓ ህብረት የተናገረውን ምስክርነት ተመልከቱ ይላል። ይበጅ ብያለሁ! ከዚህ በፊት ለዳዊት ከበደ(አውራምባ ጋዜጠኛ) እልል በሉ ተብለን በኢሳት ቀርቦ እንዲሁም ሌሎች ሌሎች ተደርጎ አጨብጭበናል። ይህም ይሁን ዝናን የማይፈልግ ኢትዮጵያዊ ቁጥር በጣም ጥቂት ስለሆነ… ፕሮፌሰር…ዶክተር….ተመራማሪ…..ኢንጅነር…አንጋፋው ጋዜጠኛ…አንጋፋው አርቲስት… ወዘተ ብዙ ዝና አለን። ብዙ የነጻነት ታጋዮች፣ ወታደሮች የሉንም ቢኖሩም ጥቂትና እነሱንም ማጥፋት የተለመደ እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል ባህሪያችን ነው። ምክንያቱም እነዚህ የነጻነት ታጋዮች ከዶክተሮቹ ከሰበአዊ መብት ተሟጋቾቹ መብለጥ የለባቸውም በሚል አናሳ አስተሳሰብ ነው። ቆብ ሌላ ተግባር ሌላ።
ወያኔ በሚሰጠን የቤት ስራ እየተዘናጋን ስራ ፈቶችን ሰብስቦ ትግሉ አንድ እርምጃ ወደፊት እንዳይራመድ እንባላ ዘንድ ማእረግ ባላቸው ሰዎች የምቀኝነትን መርዝ ማሰራጨት ይጀምራል። እኛ ደግሞ እንመቻቻለን። የነጻነት ትግል መንገዱን ወጣ ገባ ለማደረግ ያልተተባ፣ ያልተገራ ብእራችንን አንስተን “ግንቦት 7 ሆይ ፍረስ ወያኔ የጀመረን ይጨርሰን፣ ተዋርደን መገዛታችን እንቀጥል ዘንድ ወታደሮችህን ጋዜጠኞች አድርጋቸውና የዜና ሀተታ ይስሩልን” እንላለን።
እኔ ግን ከቻልን ትግሉን መቀላቀል ካልቻልንና እውነተኛ የኢትዮጵያ ህልውና እንዳትፈራርስ የምንፈልግ ከሆንን እሲት ገለል እንበል። ለወያኔ ብቻ ሳይሆን ለግንቦት ሰባትም፡፡ ማናችንም ቢሆን ብእርን አንሰተን ዌብሳየት ፈጥረን የምንታገለውን መሰዋእት ሳይሆን፤ እንደ እየሱስ ክርስቶስ በሞታቸው ድነትን፣ በደማቸው ነጻነትን፣ በአጥንታቸው ክብርን ሊመልሱልን ከበርሃ ማዶ ድቅድቅ ባለ ጨለማ የኢትዮጵያን ኤሎሄ ሰምተው ዳር ሳይሆን እሳት ላይ ያሉትን ጀግኖች ከእነ ችግራቸው በርቱ ከማለት ፈራርሱ ብሎ ማለቱ ማን ነኝ እኔ ማን ነው እሱ? እንበል እኔ ማጨብጨብ ደክሞኛል።
ስለዚህ ጸሃፊውና ብእሩ ምነው በዴሞክራቲክ በተባለው የወያኔ ግሩፕ ላይ አተኩሮ ሀገራችንን አደጋ ውስጥ የከተታትን ‘እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይበቅል’ ያለቸውን አህያ ነጭና ጥቁር አሊያም ቢጫ መሆኗን በካበቱት ልምዳቸው ለምን አላዩልንም ወይስ ይሄን አይጋ ፎረም ላይ አገኘዋለሁ?
በአኬልዳማ ድራማ ወያኔ ይህንን ጸሃፊው አሁን ያሉንን “የብዙ ወጣት ኢትዮጵያዊያኖችም ሕይወት በዚህ መያዣና መጨበጫ በሌለው የግንቦት 7 ቅዥት ተደናቅፏል” የሚለውን ዜማ ደጋግመን ሰምተናል። አብዛኞቻችን አይ ወያኔ እና ኢቲቪ ብለን እሰየው ግንቦት 7 በርቱ ወያኔ እንቅልፍ አጥቶ ሌሊት እየተነሳ ድራማ መስራት ጀምሯል አልን፤ ደገፍናቸውም። ታዲያ ወያኔና አጫፋሪዎቹ በደነገጡ ቁጥር ስራ ሳይሰራ ይቅር? ኧረ ግንቦት ሰባቶች ይህን ሰምታችሁ ቅር እንዳትሰኙ። በአማራው ፕሬዝዳንት ለሃጫም አማራ፣ ማንነቱን የማያውቅ ጫማ የሌለው ህዝብ፣ በሶማሊያው ፕሬዝዳንት አማራው ና ኦሮሞው እንዳየተባበሩ ትግሬውን ውደዱ፣ ከደቡብ ደግሞ አማራውን አስወጡ፣ ዋልድባን አፍርሱ… ዜጎቻችን ህገ-ወጥ ናቸው በሳውዲ ይገደሉ… እኮ የትኛው ይሆን ግንቦት 7 ፈጽሞት እንታገለው የምንለው? ኧረ ጎበዝ ማንነው የምንታገለው? በዳዩን ወይስ ተበዳዩን?
በርግጥ ነው ዝና የሚፈልጉ ሰዎች ወይም እኔ ያልኩት ካልሆነ የሚሉ ሰዎች ብእራቸውን አንሰተው አንዴ ስለ ግንቦት 7 የውጪ ፖሊሲ ሌላ ግዜ ደግሞ ስለ መከረኛው የህዝብ ልሳን “ኢሳት” ላይ መጎንተራቸው አልቀረም። ይህም ባልከፋ የአጻጻፉ ዘይቤ ወይም የትረካው አጨራረስ ግን ምን አለበት አንድ ሆነን እንደ ግንቦት 7 መረር ብለን “ታላቁን’ ህወሃት እንጥለው ዘንድ አመስግነው ቢዘጉት፤ ከፈቶ ከማበላሸት ይልቅ።
ልጨርስ “ነፃነትን የማያውቁ ነፃ አውጪዎች’ መሆን ይከብዳል። ስለዚህ በእኔ እምነት ግንቦት ሰባት የሚባለውን ሁሉ እያዳመጠ ሙያ በልብ ብሎ እንደሚሰራ አልጠራጠርም። ዶክተሮችም፣ ፕሮፌሰሮቹም፣ ኢንጅነሮችም፣ ወታደሮቹም አሉት ለየት ከሌላው የሚያደርጋቸው ማእረጋቸው ሳይሆን ለተነሱለት አላማ መጠመዳቸው ለተግባራዊ ስራ መፍጨርጨራቸው ነውና ተግባርን እናስቀድም፤ ከዛ ደግሞ እንተቻቸው። ትችት ጥሩ ነው ግን ከቅንነት ጋር ሲሆን ይጠቅማል፡፡ ስለዚህ ጠላታችን ወያኔ ነው!!! ብእራችን፣ ገንዘባችን፣ ጉልበታችን ሁሉ ለነጻነት ለሚደረጉ እልህ አስጨራሽ ትግል የሚረዱ ጋሻዎች ይሁኑን እላለሁ።
ህዝባዊ ሃይሉም በርታ! የማንችል ደግሞ አምላክ ጩኸታችን ሰምቶ ሀገራችንን የሰላም የደስታና የነጻነት ሃገር ያድርግልን ዘንድ እንጸልይ። የምንችል ደግሞ አንድ ሁነን ትግሉ ውስጥ እንግባና እንደህዝባዊ ሃይሉ እምቢ ለነጻነቴ፣ ለሀገሬ እንበል!!! ነገር ግን እምቢ ለወሬ……http://ecadforum.com/Amharic/archives/10949/
No comments:
Post a Comment